ለፀጥታ
መደፍረስ ምክንያት የሆኑ
ፀጥታ አደፍራሽ ሀይሎች
መንግስት ቢያውቃቸው እንጂ
የኢትዮጵያ አያውቅም ።
ህዝብ ካላወቀ ደግሞ ከመንግሥት
ጋር መተባበር አይችልም
። በመሆኑም ማህበራዊ
ችግሮች ከመቀነስ ይልቅ
እየተባባሱ የመሄድ አጋጣሚ
መፈሩ አይቀርም ። መንግስት
ወቅታዊ እንዲሁም በቂ
መረጃ ለህዝብ አይሰጥም
። ህዝብ መረጃ የማግኘት
መብቱ ሲነፈግ የፀጥታና
መረጋጋት ችግር ይስፋፋል
። መንግስት ባለቤት የሌለው
አጀንዳ እያናፈሰ የህዝብ
ሰላም ያውካል ። በምዕራብ
ሆነ በምስራቅ ፣ በሰሜን
ሆነ እንዲሁም በደቡብ
የአገርና የህዝብ ደህንነት
ስጋት ለይቶ ለህዝብ የማሳወቅ
የመንግስት ሀላፊነት ነው
። ህዝብ በአገሩ የሚፈፀሙ
የፀጥታ ስጋቶች የማወቅ
ሙሉ መብት አለው ። ህዝብ
ሰለ አገሩ ሁለንተናዊ
እንቅስቃሴ ይበልጥ ባወቀ
ቁጥር ሰላሙን የማስጠበቅ
ሀላፊነቱ ይወጣል ።
ጠቅላይ ዶክተር
አብይ አህመድ ወደ ስልጣን
ከመጡ ጀምሮ በለውጥ ሰም
የታሰሩ እና የተገደሉ
ኢትዮጵያውያን ቁጥር በቀላሉ
የሚገመት አይደለም ።
በተለይ በአዲስ አበባ
ከተማ ከመሬት ይዞታ እንዲሁም
የንግድ ስርአትና ዝውውር
ጋር በተያያዘ በትግራይ
ተወላጆች ላይ የደረሰ
እስራትና መንገላታት ተገቢ
አልነበረም ። አህያውን
ፈርቶ ዳውላው እንደሚባለው
መሬት ሲሸጡ ሲለውጡ የነበሩ
ባለስልጣናት ተጠያቂ ሳይሆኑ
የግለሰቦች ንብረትና ሐብት
እንዲታገድ መደረጉ ተገቢ
አልነበረም ። በምዕራብ
ኢትዮጵያ የመንግስት ሆነ
የግል ባንኮች በኦነግ
ታጣቂዎች ሲዘረፍ ፣ ንፁሃን
ሰዎች ሲገደሉ መንግስት
እንዳልሰማ ማለፉ ከትዝብት
በላይ ነበር ። ዜጎች በአገራቸው
ተፈናቃይ እንዲሆኑ መሆን
ከመንግሥት አልባ አገር
እንኳን የማይጠበቅ ድርጊት
ነበር ። በኮዮፈች የጋራ
መኖሪያ ቤቶች የቤት ባለቤት
እጣ እድለኞች በጃዋር
መሐመድ አማካይነት እደላው
እንዲቆም መደረጉ እንዲሁም
ጉዳዩ በጠቅላይ ሚኒስትር
የዘር የፖለቲካ ድርጅት
መደገፉ አሰገራሚም አሳዛኝም
ነበር ። ያ ክሰተት ጠቅላይ
ሚኒስትር አብይ አህመድ
የህዝብ መሪ ለመሆናቸው
አጠያያቂ ነበር ። የአማራ
እና የትግራይ አገናኝ
መንገዶች በስርአት አልባ
የመንግስት ሀላፊዎች ሆኑ
ግለሰቦች ሲዘጉ የጠቅላይ
ሚኒስትር አሰተዳደር ምንም
የማስተካከያ እርምጃ ያለመወሰዱ
የመንግስት የማስፈፀም
አቅም መሽመድመድ የሚያመላክት
ነበር ።
ኢትዮጵያ እንደ
አገር እንዲሁም የኢትዮጵያ
ህዝብ እንደ ህዝብ ከመበልፀግ
ይልቅ መደህየት ፣ ከመደጋገፍ
ይልቅ መጠላለፍ ፣ ከመከባበር
ይልቅ መጠላላት ፣ ከአንድነት
ይልቅ መነጣጠል ፣ ከመተሳሰብ
ይልቅ ፣ መጎዳዳት እንዲያቆጠቁጥ
አንዱ ምክንያት ለሴራ
ፖለቲካ ተገዢ መሆን ይመስለኛል
። የፖለቲካ ሰልጣን ለመያዝ
መገዳደል ለምን አስፈለገ
? ። ወንድም ወንድሙን አጥፍቶ
የመንግስት ስልጣን ለመጨበጥ
ማሰቡ በራሱ አብይ ስህተት
ነው ። የመንግስት ስልጣን
የህዝብ መሆኑ የሚያምኑ
ፖለቲከኞች የሴራ ፖለቲካ
ስንክሳር ውሰጥ መነከር
ኪሳራ ቢሆንም እንጂ ትርፍ
አይኖረውም ። የሴራ ፖለቲካ
አገር አፍራሽ ፣ ትውልድ
ጨራሽ ፣ ህዝብ በታኝ ፣
የአገር ልማት አውዳሚ
፣ የድህነት መነሻ ፣ የማህበራዊና
ኢኮኖሚያዊ ግጭት ምክንያት
፣ የኋላቀርነት ማሳያ
ምልክት ነው ። በሀሳብ
ልዕልና ተከራክሮ ፣ በህዝብ
ይሉኝታና ተቀባይነት አግኝቶ
የመንግስት ሰልጣን ከመያዝ
በጠበንጃ አፈሙዝ ስልጣን
ላይ ለመውጣት ማሰብ የዋህነት
ብቻ ሳይሆን አገራዊ ወንጀል
ነው ። በሴራ ፖለቲካ የመንግስት
ሰልጣን የሚጨበጥ መንግስት
በህዝብ ፈፅሞ ተቀባይነት
የለውም ። የፖለቲካ ስልጣነ
የህዝብ አሰተዳደር በመሆኑ
የህዝብ ይሉኝታ ያሰፈልጋል
። የሴራ ፖለቲካ መጠንሰሰ
የህዝብ ውሳኔ መግታት
በመሆኑ በምንም መልኩ
ተቀባይነት የለም ። ሰኔ
15 ቀን 2011 ዓ.ም በአማራ ክልል
ባህርዳር ከተማ የተፈፀመው
በጅምላ የክልሉ ባለስልጣናት
የመረሸን ተግባር የተወገዘ
ሲሆን መላ የኢትዮጵያ
ህዝብ ያስቆጣ አሳዛኝ
ድርጊት ነው ። ድርጊቱ
በምንም ማሳያ ኪሳራ እንጂ
ትርፋማ አልነበረም ።
በእኔ አተያይ በባህርዳርና
አዲስ አበባ የተፈፀመው
የግድያ ወንጀል የመፈንቅለ
ሰርአት እንደነበር ስምምነት
የለኝም ። የሰኔ 15 ቀን በአማራ
ክልል በህዳር ከተማ እንዲሁም
የኢትዮጵያ ዋና ከተማ
አዲስ አበባ ላይ የተፈፀመው
አሳፋሪና አሳዛኝ የሴራ
ፖለቲካ ወንጀል በገለልተኛ
አጣሪ ኮምሽን መመርመር
እና መጣራት አለበት የሚል
እምነት አለኝ ።
የጠቅላይ ሚነስትር
ዶክተር አብይ አህመድ
አስተዳደር የ 2011 የበጀት
አመት ዝርዝር የሥራ አፈፃፀም
ለኢትዮጵያ ህዝብ ተወካዮች
ምክርቤት ባቀረቡበት ወቅት
ወቅታዊ የኢትዮጵያ ጉዳይ
ከምክር ቤቱ በጥያቄ መልክ
ተነስቶ ነበር ። ጠቅላይ
ሚንስትር ዶክተር አብይ
አህመድ የመንግስት ትዕግሥት
እሰከ አገራዊ አንድነት
ድረስ እንደሆነ ነገር
ግን የአገር ልዕልና እንዲሁም
የህዝብ ደህንነት የሚፃረር
ሁሉ አሰፈላጊ መንግሰታዊ
እርምጃ ይወሰዳል ሲሉ
ተደምጧል ። በክልሎች
ከተሞች ሆነ በአዲስ አበባ
ከተማ ሰዎች በገፍ እየታሰሩ
እንደሆነ የሰማል ይታያል
። በእኔ እምነት ጠቅላይ
ሚኒስትር ዶክተር አብይ
ህግን መሠረት ያደረገ
እርምጃ ለመውሰድ ዘግይቷል
የሚል እምነት አለኝ ።
ነገር ግን ጠቅላይ ሚኒሰትሩ
ጠበንጃ አንግበን እንዋጋለን
ሲሉ የኢትዮጵያ ህዝብ
ተወካዮች ምክርቤት አባላት
ሀሳቡን በጭብጨባ ሲደግፉት
ማየቴ በሁሉም ባይሆን
ደጋፍ በሰጡ የምክር ቤቱ
አባላት ላይ አዝኛለሁ
። ለምንና እንዴት ብሎ
ከመጠየቅ ይልቅ ግደል
ብሎ ድጋፍ መሰጠት ከምክር
ቤት አባላት የሚጠበቅ
አልነበረም ። የኢትዮጵያ
ጠቅላይ ሚኒስትር ተጠሪነቱ
ለኢትዮጵያ ህዝብ ተወካዮች
ምክር ቤት ሆኖ ሳለ ምክርቤቱ
ለጠቅላይ ሚኒስትሩ እስኪመስል
የወረደ የልጅ ጨዋታ ነበር
የታዘብኩት ። መንግስት
ህግን መሠረት አድርጎ
ወንጀል መከላከል ሲቻል
ሀይል እጠቀማለሁ ሲል
ማጨብጨብ ለምን አስፈለገ
። የኢትዮጵያ ህዝብ ተወካዮች
ምክር ቤት ወንበር መቶ
በመቶ በኢህአዴግ የተያዘ
ነው ። በመሆኑም የሀሳብ
ልዩነት ፍጭት የማይታይበት
ደካማ ምክርቤት ነው ።
ህዝብ ከህግ ውጭ በሐይል
ማስተዳደር ሰላምና መረጋጋት
አያመጣም ። ህዝብ ለህግ
ካልተገዛ ለሐይል አይገዛም
። በመሆኑም የተረጋጋ
አገር ለመፍጠር ህግን
መሠረት በማድረግ ወንጀል
መከላከል ይቻላል ። ችግሩ
የፍትሕ ተቋማት ገለልተኛ
ካለመሆን ጋር በተያያዙ
የሚፈጠሩ ማህበራዊ ችግሮች
ውስብስብ ከመሆናቸውም
በላይ ፍትሀዊ የህግ አሰራር
እንዳይኖር ምክንያት ይሆናል
። ለህዝብ ታማኝ ያልሆነ
መንግስት አገራዊ ችግሮች
በቀላሉ መፍታት አይችልም
። የህዝብ ደህንነት የማያስጠብቅ
መንግስት በትናንሽ አጀንዳዎች
ጊዜ ከማጥፋት ውጭ የህዝብ
ፍላጎት አያሟላም ። በመሆኑም
መንግስት ህዝብ በማያምንበት
ጉዳይ ጊዜ ማባከን የለበትም
። የህዝብ ፍላጎት ሰላምና
መረጋጋት መስፈን ነው
። የህዝብ ፍላጎት የመንግስት
ፍላጎት ከሆነ ህዝብ የሚጠይቀው
መንግስት ማስተካከል አለበት
። የጠቅላይ ሚኒስትር
ዶክተር አብይ አህመድ
አስተዳደር የኢትዮጵያ
ህዝብ አይንና ጀሮ መሆን
ላይ መሸራተት ይታይባቸዋል
። የህዝብ ድምፅ በአግባቡ
አይሰማም ፣ አይመዘንም
፣ ተግባር ላይ አይውልም
።
በኢትዮጵያ ከፍተኛ
የመንግስት ሀላፊዎች ላይ
ለተፈፀሙት ከፍተኛ የግድያ
ወንጀሎች የጠቅላይ ሚኒስትር
ዶክተር አብይ አህመድ
በቀጥታ ሆነ በሌላ ከተጠያቂነት
ውጭ አይሆንም ። ታላቁ
የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ
መሐንዲስ በግፍ መገደል
ገና ያልተጣራ ጉዳይ ነው
። የአማራ ክልል አሰተዳደር
ከፍተኛ የሥራ ሀላፊዎች
የጭካኔ ግድያ ከአማራ
ዲሞክራሲ ፖርቲ ካድሬዎች
አሰተያየት ውጭ በቂና
ገለልተኛ መረጃ አልተገኘም
። የኢትዮጵያ ከፍተኛ
የጦር አዛዥ በግፍ መገደል
ከገለልተኛ አካል መረጃ
ገና አልተገኘም ። በግድያ
ሴራ ላይ የመንግስት እጅ
ይኑር አይኑር በገለልተኛ
የተጣራ መረጃ የለም ።
ጉዳዩ በገለልተኛ ካልተጣራ
መንግስት በሚሰጠው መረጃ
ብቻ ተመሥርቶ ትንታኔ
ለመስጠት የሚቻል መስሎ
አልታየኝም ። ምክንያት
እውነት ከቤተመንግስት
ይገኛል ብሎ መጠበቅ የዋህነት
ነው ።
?
። የኢትዮጵያ መከላከያ
የበላይ ሀላፊ ጀነራል
ሰዐረ መኮነን እንዴት
በቅርብ ጠባቂው ይገደላል
? ። የአማራ ክልል ርዕስ
መስተዳድር ለመግደል ሴራ
ሲጠነሰሰ የኢትዮጵያ የደህንነት
መሥሪያ ቤት ጉዳዩ እንዴት
ሳያውቀው ቀረ ? ።
በኢትዮጵያ የፖለቲካ
የሐሳብ ልዩነት ምክንያት
መገዳደል ማብቃት ያለበት
ጊዜ ይመስለኛል ። የኢትዮጵያ
ፖለቲከኞች ባለቤት አልባ
አጀንዳዎች እንዲሁም ውጤት
አልባ የሴራ የፖለቲካ
አካሔድ ማቆም ፍትሀዊነት
ነው ። ክብር ነክ የትንኮሳ
ንግግር አለፍ ሲልም የዘር
ፖለቲካ ማራመድ ማቆም
ፍትሐዊነት ነው ። ህዝብ
የሚያከብር ፣ለህዝብ ደህንነት
ጥብቅና የሚቆም ሀቀኛ
የፖለቲካ ድርጅት እንዲያቆጠቁጥ
፣ የዲሞክራሲ መርህ ተኮር
የፖለቲካ ሰርአት እንዲያብብ
ከተፈለገ በህግ ልዕልና
የሚመራ ህዝብና መንግስት
መኖሩ የግድ ይሆናል ።
መንግስት ህዝብ ገዳይ
፣ ህዝብ ደግሞ መንግስት
ገዳይ ከሆነ አገርም ህዝብም
አይኖርም ። በመሆኑም
ለህግና ሰርአት ልዕልና
የቆመ መንግስት ያሰፈልጋል
። ህዝብና መንግስት መናበብና
መግባባት ካልቻሉ የችግር
መነሻ ይሆናሉ ። አገር
በህግ የበላይነት እንጂ
በአድርባይ የፖለቲካ ድርጅት
ካድሬዎች አይመራም ።
የፖለቲካ ድርጅት ካድሬዎች
ከህግ በላይ ሆኖ ዜጋ ሲበድሉ
እርምጃ የማይወስድ መንግስት
ለህዝብ አስተዳደር አይደለም
የሞተ እሬሳ ለመቅበርም
ብቁ አይደለም ። መንግስት
የሚወስዳቸው የእርምት
እርምጃዎች ለህዝብ አይገልጽም
። በመሆኑም በኢትዮጵያ
ወንጀለኛና ንፁህ መለየት
አይቻልም ። አውራ ጎደና
የጭነት መኪና አስቁሞ
የሚዘርፉ የተደራጁ ስርአት
አልባ ሰዎች መንግስት
ተከታትሎ ለህግ ማቅረብ
ሥራው ነው ። ሰላምና መረጋጋት
ማስፈን ተቀዳሚ የመንግስት
ሰራ ነው ። ልማት ማፋጠን
፣ የአገር አንድነት ማስጠበቅ
፣ የህዝብ ድህነት ማስከበር
፣ ሥራ አጥነት መቀነስ
፣ ሁሉም አይነት ወንጀሎች
አሰቀድሞ መከላከል መንግስት
ከህዝብ የተቀበለው ሀላፊነት
ነው ።
የጠቅላይ ሚኒስትር
ዶክተር አብይ አህመድ
አሰተዳደር በበርካታ ችግሮች
የተከበበ ቢሆንም የችግሮች
መፍትሔ ደግሞ ራሱ መንግስት
ነው ። ያለአግባብ በአዲ
አበባ ከተማ የታሰሩ በርካታ
የትግራይ ተወላጆች በአስቸኳይ
መፈታት አለባቸው ። የአማራ
ህዝብ እና የትግራይ ህዝብ
በጠላትነት እንዲተያይ
ጥላቻ የሚሰብኩ የኢህአዴግ
ካድሬዎች ከድርጊታቸው
መታቀብ የግድ ይላቸዋል
። የአማራ አሰና የትግራይ
ህዝብ ወንድም ህዝብ እንጂ
የቆየ ቅራኔም ሆነ ቂም
በቀል ያልተላበሰ ህዝብ
ነው ። የሁለቱም ህዝብ
የፖለቲካ ካድሬዎች ህዝብ
የሚያቀራርብ ተግባራት
ከመፈፀም ይልቅ አሉባልታ
ላይ ተሰማርቶ ይታያል
። ይህ አስነዋሪ ድርጊት
እንዲቆም ይፈለጋል ።
በውይይት እንጂ በጉልበት
የሚፈታ ጉዳይ የለም ።
የአማራ ክልል ሆነ የትግራይ
ክልል አመራሮች እየፈፀሙት
ያለ የተሳሳተ የፖለቲካ
ቁማር ተገቢነት የለውም
። መሬት የሰው ህይወት
አይተካም ። የሐይል አሰራር
ማንንም አያስተምርም ፣
ምንንም አያሰወግድም ።
ትርፉ ትርምስና መተላለቅ
ብቻ ነው ። ችግሮች ከጥላቻ
በራቀ መንፈስ ለመፍታት
መትጋት የአንድ መሪ ብልህነት
ነው ። በቅርቡ የአማራ
ክልል ምክርቤት ያስተላለፈው
አስቸኳይ ውሳኔ በሚገባ
የተሞከረበት ሳይሆን ከስሜታዊነት
የመነጨ ውሳኔ ይመስለኛል
። የትግራይ ልዩ ሐይል
ከአማራ አዋሳኝ ቦታዎች
እንዲለቅ የሚል ሲሆን
መቀሌ የመሸገው አጥፊ
ሐይል ብሎ መፈረጅ አግባብነት
የለውም ። በአንድ አገር
እየኖሩ ፣ በአንድ አይነት
ቋንቋ እየተግባቡ ፣ እንደ
ባላንጣ መተያየት አግባብነት
የለውም ። መስክን ያሰፈልጋል
። ከክብር ነክ የጥላቻ
ንግግሮች መቆጠብ ያሰፈልጋል
። መቀሌ የመሸገው ሐይል
ለኢትዮጵያ አንድነት ችግር
መስሎ አይታየኝም ። ምክንያቱም
ሁሉም ኢትዮጵያውያን በመሆናቸው
ሁሉም የኢትዮጵያ ዜጋ
የሚያስበው መሳብ የሚችሉ
ሰዎች ናቸው ። የፖለቲካ
ልዩነት ቢኖራቸውም ክፋት
የለውም ። ሀሳብን በሐሳብ
መሞገት ተፈጥሯዊም ህገ
መንግሰታዊም ነው ።