ከሰሞኑን የአለም የሰብአዊ መብት ተማጓቹ አልመስቲ ኢንተርናሽናል በኢትዮጵያ በኦሮሚያ እና በአማራ እየተፈፀመ ያለውን የሰብአዊ መብት ጥሰት አስመልክቱ ያወጣው ሪፖርት በተለያዩ ሚድያዎች የተሰጠው አስተያያት የእውነት ግርምትን ፈጥሮብኛል፡፡

የአሁኑ አመራር ሆነ የቀድመዎ አንድ ከሚያደርጋቸው ነገሮች መካከል በተለያዩ አለማቀፍ ሚድያዎች የሚወጡ ሪፖርቶች ማጣጣላቸው ነው፡፡ እርግጥ ነው ዛሬ በአገራችን መንግስት የፈጠረው ችግር መሰረት አድርጎ ከማስተካከል ይልቅ፣ ፖለቲካው ወደ ፖለቲካዊ ብሽሽቅ ተቀይሮ ቀጥሏል፡፡

ሚድያዎቻችም እውነታውን መርምሮ እና አገናዝቦ ከመዘገብ ይልቅ ሁልጊዜ እና ምንግዜም የፖለቲካ ፓርቲዎች መላስ መሆናቸውን በድጋሚ አስመስክረዋል፡፡

በአገራችን ሞቶ የሚለቀስለት ወይም የሰው ሞት የሚሆነው እንደ ገዥው ፓለቲካ ይሆንታ መሆን ከጀመረ ሰንብቷል፡፡የሰው ሞቱ ሰሚ መንግስት እና ፖለቲካ መሪ ካለው ሞቱ የሰው ሞት ሆኖለት ይዘመርለታል ብሎም ይጮሁለታል፡፡ በተቃራኒው የሰው ሞቱ የሚሰማ መንግስት ከሌለው ደግሞ የሰው ሞት መሆን ቀርቶ እንደ ዝንብ ሳይቆጠር በዛው የውሃ ሽታ ሆኖ ይቀራል፡፡

የመንግስት ደጋፊ የሆኑ ሚድያዎች የወጣው ሪፖርት ሆን ተብሎ የተቀነባበረ እና የግብፅ እጅ እንዳለበት ብሎም የወያኔ ሴራም አንድ ላይ የተጨመረበት እንደሆነ ዘግበዋል፡፡

Videos From Around The World

ከኢሳት ሚድያ መሳይ የተባለ ጋዜጠኛ
Full Website